...

ኮርፖሬሽኑ እና የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

ቀን: Oct 21, 2024

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢኮሥኮ) እና የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ቃሊቲ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ ፓራዳይዝ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጥቅምት 11 ቀን 2017 . የሁለቱም ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የፊርማ ሥነ-ስርዓቱን ያካሄዱት በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በኩል የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ሲሆኑ በኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በኩል ደግሞ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራቱ ናቸው።

የመግባቢያ ስምምነቱ የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ

...

የኮርፖሬሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበሩ

ቀን: Oct 21, 2024

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች 17ኛውን ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ፡፡

 

አመራሮቹና

...

የአፍሪካ ምህንድስና ድርጅቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ኮርፖሬሽኑን ጎበኙ

ቀን: Oct 21, 2024

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአፍሪካ ምህንድስና ድርጅቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ኢንጅነር ካዛዋዲ ፓፒያስን እና ኢንጂነር ማርቲን ማኑሃዋ የፌዴሬሽኑ የቀድሞው ፕሬዚደንትን በዋና መስሪያ ቤቱ በክብር ተቀብሏል። ፕሬዚደንቶቹ የኮርፖሬሽኑን የቢም ፕሮጄክት መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት የልህቀት ማዕከል፣ የኮንስትራክሽን ሙያተኞች ማበልጸጊያ ኢንስቲትዩትን፣ የኢሲሲ-ኢንዱስትሪ ዞን እና የኮንስትራክሽን ማቴሪያል ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ በርካታ ዋና ዋና ተቋማትን ጎብኝተዋል።

ፕሬዚዳንቶቹ ኮርፖሬሽኑ በተለያዩ ዘርፎች ባሳየው አዳዲስ ፈጠራዎች እና የላቀ አፈፃፀም  ተደንቀዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ዮናስ አያሌው መሪዎቹን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለው ከተቀበሉ በኋላ ኮርፖሬሽኑ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የኮንስትራክሽን መስኮች አሰራሮችን በማሳደግ ረገድ እያከናወነ ያለውን ለውጥ አስረድተዋል።

...

ኮርፖሬሽኑ ከደቡብ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጋር የዲዛይን ሥራዎችን ለመሥራት

ቀን: Oct 21, 2024

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (...) በደቡብ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በስድስቱ ክላስተር ማእከላት ለሚገነቡ

...

Corporation launches training institute, digital technology centre

ቀን: Nov 30, -1

በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 7፣ ቤቴል መንዲዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ3.3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የተከለሠ የኮንትራት ዋጋ እየተገነባ ያለውን ኮልፌ ቀራኒዮ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክትን እስከ 2016 በጀት ዓመት መጨረሻ ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለባለቤቱ ለማስረከብ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ፡፡

ግንባታው 2013 በጀት ዓመት መጨረሻ ሐምሌ ወር ላይ የተጀመረውን ይህን ፕሮጀክት እስከ 2016 በጀት ዓመት መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በሥራ ተቋራጩ፣ በባለቤቱ እና በሌሎች ባለድርሻ አካላት በኩል ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ሥራዎች በርብርብ እየተሠሩ እንደሆነ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መረሳ ተስፋየ ገልፀዋል፡፡

ቀደም ሲል ከክፍያ ጋር በተያያዘ ለአራት ተከታታይ ወራት ግንባታው ቆሞ እንደነበር የገለፁት ኢንጂነር መረሳ ተስፋየ አሁን ላይ ችግሩ በመቀረፉ ሥራው በከፍተኛ ፍጥነትና ቁርጠኝነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት፡፡

ፕሮጀክቱን በታቀደው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለባለቤቱ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ቢሮ፣ ለማስረከብ ፕሮጀክቱ በሁለት ሎት ተከፍሎ በሁለት ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅና በሁለት ፈረቃ ማለትም 24 ሰዓት እየተሠራ እንደሆነ ነው ኢንጂነር መረሳ የገለፁት፡፡

ኢንጂነር መረሳ ተስፋየ ከዚህም ሌላ የሰው ኃይል በመጨመርና 17 ያህል ንዑስ ተቋራጮችንና የጉልበት ሥራ ተቋራጮችን በማስ

...

ፕሮጀክቱን ከተያዘለት ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው

ቀን: Nov 30, -1

በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 15፣ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ፣ ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የተከለሠ የኮንትራት ዋጋ እየተገነባ ያለውን የአዲስ አበባ ከተማ መግቢያ እና መውጫ የግብርና ውጤቶች ማዕከልን ከተያዘለት ጊዜ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሆነ ተገለፀ፡፡

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 20 ቀን 2020 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2023 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ኮርፖሬሽኑ ከፕሮጀክቱ ባለቤት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ቢሮ ጋር ውል መዋዋሉን የገለፁት የፕሮጀክቱ ሎት 1 ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዓለምአየሁ ካሣ ከተያዘለት የኮንትራት ጊዜ ቀድሞ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ኢንጂነር ዓለምአየሁ ፕሮጀክቱን ከተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ቀድሞ ለማጠናቀቅ በኮርፖሬሽኑ፣ በባለቤቱ እና በአማካሪ ድርጅቱ በኩል ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሆነ እና ለዚህም በየጊዜው የክትትል፣ ቁጥጥር እና ድጋፍ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

አሁን ላይ የፕሮጀክቱ የፊዚካል አፈፃፀም 70 በመቶ መድረሱን የተናገሩት ኢንጂነር ዓለምአየሁ ካሣ ፕሮጀክቱን ከኮንትራት ጊዜው አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ሥራው በሁለት ሎት ተከፍሎ በሁለት ሥራ አስኪያጆች እየተከናወነ፣ ከመደበኛ ሠራተኞችና የሥራ ሠዓት በተጨማሪ ንዑስ ሥራ ተቋራጮችን በማስገባት እና ተጨማሪ ሠዓት በመጠቀም እየተሠራ መሆኑን፤ የፕሮጀክቱ ባለቤትም ክፍያዎችን ሳያቆራርጥ እየፈፀመ እንዲሁም አማካሪ ድርጅቱ ከፍተኛ ክትትል እና ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ሎት 2 ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አንዋር ንጉሤ በበኩላቸው በሎት 2 ሥር ያሉትን እንደ የአስተዳደር ህንፃ፣ የጅምላ መሸጫ ሱቆች፣ መጋዘኖ