...

ኮርፖሬሽኑ በሦስት ዓለም አቀፍ የሥራ አመራር ሥርዓቶች ላይ ስልጠና ሰጠ

ቀን: Nov 30, -1

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) ለሠራተኞቹ በሦስት የዓለም አቀፍ የሥራ አመራር ሥርዓቶች ላይ ስልጠና በመስጠት ሥርዓቶቹን በሥራ ላይ ሊያውላቸው እንደሆነ ተገለጸ፡፡

 በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ኃላፊ አቶ አመንቴ ዳዲ በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ የተጀመረውን ስልጠና ሲከፍቱ እንደተናገሩት ኮርፖሬሽኑ ምርትና ምርታማነቱን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ በርካታ የሪፎርም ፕሮግራሞችን እና የተቀናጀ የሥራ ዓመራር ሥርዓትን ተግባራዊ እያደረገ ነው፡፡

 ኮርፖሬሽኑ እስከ አሁን ድረስ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን (ISO: 9001/2015) ፣ የአካባቢ ጥበቃ ሥራ አመራር ሥርዓትን (ISO: 14001/2015) እና የሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓቶችን (ISO: 45001/2018) ተግባራዊ እንዳደረገ እና የዕውቅና ምስክር ወረቀት እንዳገኘ ተናግረዋል፡፡  

 ኮርፖሬሽኑ በያዝነው የበጀት ዓመትም አራት ተጨማሪ የዓለም አቀፍ የሥራ አመራር ሥርዓቶችን ማለትም የአደጋ ሥራ አመራር ሥርዓትን (ISO: 31001)፣ የላቦራቶሪ ሥራ አመራር ሥርዓትን (ISO: 17025) ፣ የንግድ ሥራ አመራር ሥርዓትን (ISO: 22301

...

Big 5 Global Construction Exhibition kicks off

ቀን: Nov 30, -1

The annual Big 5 Global Construction Exhibition has officially been opened at Dubia World Trade Center in the United Arab Emirates.

Ethiopian Construction Works Corporation is among the thousands of exhibitors in this annual hub for the global construction industry which attracts attendees from more than 150 countries.

By being an exhibitor, the corporation has found the event very relevant for showcasing and forging partnership in the industry.

This year's Big 5 Global Construction Exhibition lasts for the next four consecutive days.

Big 5 Global Construction Exhibition is believed to be the largest and most influential event for the construction industry.

...

Big 5 Construct Ethiopia is to be held at the end of May 2024

ቀን: Nov 30, -1

This was disclosed during an agreement signed between Ethiopian Construction Works Corporation and DMG events, a global exhibitions and publishing company with its head quarter located in Dubai, United Arab Emirates.

Engineer Yonas Ayalew, CEO of Ethiopian Construction Works Corporation and Mr. Ben Greenish, senior vice president of DMG events, signed the agreement on 5th December 2023 in Dubai.

It is to be recalled that “Addis Build by the BIG 5 CONSTRUCT ETHIOPIA” took place in May 2023 last year in Addis Ababa, Ethiopia.

The successful completion of last year's event is believed to be a precedent for hosting similar upcoming event in Ethiopia.

Meanwhile, the 2023 BIG 5 global construction show in which Ethiopian Construction Works Corporation is participating as an exhibitor is well underway with a number of events in Dubai. These include Global construction leaders’ summit held on 5th of December 2023 during which Engineer Yonas Ayalew, CEO of Ethiopian Construction Works Corporation took part.

...

ኮርፖሬሽኑ የ2016 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈጻጸሙን ገመገመ

ቀን: Nov 30, -1

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ሀብት አስተዳደር እና ሠርቪስ ዘርፍ እና ለዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ተጠሪ የሆኑ የሥራ ክፍሎች አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት የ2016 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈጻጸሙን ገመገመ፡፡

ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት 67 ፕሮጀክቶችን በ55.75 ቢሊዮን ብር እየገነባ ሲሆን ከእነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ሥራ በማከናወን 273.9 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገብ መቻሉ በቀረበው የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገልጿል፡፡ ይህም ከባለፈው የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ71 በመቶ የትርፍ ብልጫ አሳይቷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ ተቋማዊ ሪፎርሞችን በመሥራት በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉ የተገለጸ ሲሆን ከነዚህ መካከል ተቋማዊ ሪፎርም፣ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሪፎርም፣ ኢንዱስትሪያላዜሽን እና ዲጂታላይዜሽን ሪፎርም፣ ኢንተርናሽናላይዜሽን ሪፎርም እና በ2016 በጀት ዓመት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የኢንቨስትመንት ሪፎርም ሥራ ተቋሙን ትርፋማ ያደረጉ የለውጥ ሥራዎች መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡

እነዚህን የሪፎርም ሥራዎች በመሥራት የኮንስትራክሽን ግብዓት ማምረቻ ማዕከል ግንባታ፣ የERP ሲስተም፣ BIM፣ GPS፣ CCTV ቴክኖሎጂዎች ትግበራ፣ ከአገር ውጭ አዳዲስ ቅርንጫፎችን የመክፈት፣ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር አብሮ የመሥራት፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሁነቶች ላይ የመሳተፍ እና በሪል እስቴት ግንባታ መስክ የመሰማራት ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ተደራሽነቱን ለማስፋት በአገር ውስጥ በኮምቦልቻ፣ በአርባ ምንጭ፣ በጅማ እና በድሬድዋ አዳዲስ ቅርንጫፎችን የከፈተ ሲሆን በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት(IGAD) ትብብር በኬኒያ፣ በሩዋንዳ፣ በደቡብ ሱዳን እና በደቡብ አፍሪካ አዳዲስ ቅርንጫፎችን ለመክፈት እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡

በተቀናጀ ሥራ አመራር ሥርዓት(ISO 9001:2015፣ ISO 14001:2015፣ ISO 45001:2018) እውቅና ያገኘው ኮርፖሬሽኑ በሌሎችም ዘርፎች እውቅና ለማገኘት ለኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ጥያቄ ማቅረቡን በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ በካይዘን ትግበራ በርካታ ሥራዎች የተሰሩ ሲሆን በሩብ ዓመቱ ከ2 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው የካይዘን ሥራዎች ተሰርተው የኮርፖሬሽኑ ንብረቶች ጥቅም ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡ በሩብ ዓመቱ የሲሚንቶ እጥረት፣ የክፍያ መዘግየት፣ የወሰን ማስከበር፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የዲዛይን ለውጥ እና የዋጋ ግሽበት የኮርፖሬሽኑ ዋና ዋና ችግሮች መሆናቸው በሪፖርቱ ተብራርቷል፡፡

በተጨማሪም በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የ2016 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ሩብ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጓል፡፡

...

ፕሮጀክቱ በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ይገኛል

ቀን: Nov 30, -1

በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) የሥራ ተቋራጭነት ከ3.4 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የኮንትራት ዋጋ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 7፣ ቤተል መንዲዳ አካባቢ እየተገነባ ያለው የኮልፌ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡

የፕሮጀክቱ ሎት 1 ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መረሣ ተስፋዬ የፕሮጀክቱ የስትራክቸራል ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ለኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የሥራ ባልደረቦች ገልፀዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ አሁን ላይ የማጠናቀቂያ፣ የመንገድ፣ የአጥር፣ የግቢ ማስዋብ እና ሌሎች የሳይት ሥራዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተካሄዱ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

ኢንጂነር መረሣ ፕሮጀክቱን እስከ በጀት ዓመቱ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በቅርበት፣ በጥብቅ ክትትል እና ቁጥጥር እየተሠራ እንደሆነ አክለው ገልፀዋል፡፡

እንደ ኢንጂነር ገለፃ ፕሮጀክቱን በታቀደለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ያለበትን ደረጃ እና የሥራ ሂደት ወርኃዊ ዕቅድ በማውጣት በየሳምንቱ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እየተገመገመ ይገኛል፡፡

አሁን ላይ የፕሮጀክቱ የፊዚካል አፈፃፀም 64 በመቶ መድረሱን የገለፁት ኢንጂነር መረሣ ተስፋዬ ፕሮጀክቱን እስከ በጀት ዓመቱ ሰኔ 30 ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ቀን ከሌት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

የዕቃዎች የዋጋ መናር እና በገበያ ላይ አለመገኘት፣ የዲዛይንና የክፍያ ችግሮች በግንባታ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ችግሮች ሲሆኑ አሁን ላይ የዲዛይንና የክፍያ ችግሮች መፈታታቸውን ኢንጂነር መረሣ ገልፀዋል፡፡

በ24 ሺህ 500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈው ይህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 500 አልጋዎችን የሚይዙ የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶችን የሚሰጡ 14፣ 2B+G+1-4 ብሎኮችን፣ ሌሎች 4፣ G+0 ህንፃዎችን እና የሳይት ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡

ኢንጂነር መረሣ ፕሮጀክቱ ንዑስ ሥራ ተቋራጮችን ጨምሮ ለ550 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልፀዋል፡፡

ፕሮጀክቱን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንደ ሥራ ተቋራጭ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ቢሮ እንደ ባለቤት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንደ አማካሪ ድርጅት እየተከታተሉት ይገኛል፡፡

...

ፕሮጀክቱ በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ይገኛል

ቀን: Nov 30, -1

በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) የሥራ ተቋራጭነት ከ3.4 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የኮንትራት ዋጋ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 7፣ ቤተል መንዲዳ አካባቢ እየተገነባ ያለው የኮልፌ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡

የፕሮጀክቱ ሎት 1 ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መረሣ ተስፋዬ የፕሮጀክቱ የስትራክቸራል ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ለኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የሥራ ባልደረቦች ገልፀዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ አሁን ላይ የማጠናቀቂያ፣ የመንገድ፣ የአጥር፣ የግቢ ማስዋብ እና ሌሎች የሳይት ሥራዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተካሄዱ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

ኢንጂነር መረሣ ፕሮጀክቱን እስከ በጀት ዓመቱ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በቅርበት፣ በጥብቅ ክትትል እና ቁጥጥር እየተሠራ እንደሆነ አክለው ገልፀዋል፡፡

እንደ ኢንጂነር ገለፃ ፕሮጀክቱን በታቀደለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ያለበትን ደረጃ እና የሥራ ሂደት ወርኃዊ ዕቅድ በማውጣት በየሳምንቱ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እየተገመገመ ይገኛል፡፡

አሁን ላይ የፕሮጀክቱ የፊዚካል አፈፃፀም 64 በመቶ መድረሱን የገለፁት ኢንጂነር መረሣ ተስፋዬ ፕሮጀክቱን እስከ በጀት ዓመቱ ሰኔ 30 ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ቀን ከሌት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

የዕቃዎች የዋጋ መናር እና በገበያ ላይ አለመገኘት፣ የዲዛይንና የክፍያ ችግሮች በግንባታ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ችግሮች ሲሆኑ አሁን ላይ የዲዛይንና የክፍያ ችግሮች መፈታታቸውን ኢንጂነር መረሣ ገልፀዋል፡፡

በ24 ሺህ 500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈው ይህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 500 አልጋዎችን የሚይዙ የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶችን የሚሰጡ 14፣ 2B+G+1-4 ብሎኮችን፣ ሌሎች 4፣ G+0 ህንፃዎችን እና የሳይት ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡

ኢንጂነር መረሣ ፕሮጀክቱ ንዑስ ሥራ ተቋራጮችን ጨምሮ ለ550 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ገልፀዋል፡፡

ፕሮጀክቱን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንደ ሥራ ተቋራጭ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን ቢሮ እንደ ባለቤት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንደ አማካሪ ድርጅት እየተከታተሉት ይገኛል፡፡