የከባድ ተሽከርካሪዎች ጥገና
ቀን: Jan 10, 2025
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) ለተከታታይ ዓመታት ባካሄዳቸው የለውጥ ሥራዎች አማካኝነት ከተመዘገቡ ከፍተኛ ውጤቶች መካከል አንዱ በተቋሙ የኢንዱስትሪ ማናጅመንት ዘርፍ፣ በአውቶሞቲቭ እና ማሽነሪ ጥገና ማዕከል ሥር የተቋቋመው የከባድ ተሸከርካሪዎች ጥገና መምሪያ ነው፡፡
የከባድ ተሸከርካሪ ጥገና መምሪያ በሦስት ቡድኖች የተዋቀረ ሲሆን እነሱም ከባድ ተሸከርካሪዎች ጥገና፣ ሞተር ጥገና እና የተሸከርካሪዎች የአካል መገጣጠምና ቀለም ቅብ ቡድኖች ናቸው፡፡ መምሪያው በቀን ለ24 ሰዓታት በሁለት ሽፍት የሚሰጣቸው የጥገና አይነቶች ሁለት ሲሆኑ እነሱም የተሽከርካሪ አካል እድሳት እና የተሽከርካሪ አካልና የመለወጥ ሥራዎች ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት የተሽከርካሪዎች ቀለም ቅብ ሥራ የሚከናወነው “ካር ቡዝ” በተሰኘ ዘመናዊ የተሽከርካሪ ቀለም መቀቢያ ቴክኖሎጂ ሲሆን እስከ አሁን በሀገር ውስጥ ከሚገኙ የጥገና ማዕከላት ውስጥ ብቸኛው የቴክኖሎጂ ተጠቀሚ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ነው፡፡
የተሽከርካሪ አካል መለወጥ ሥራን በተመለከተ መምሪያው አገልግሎት የማይሰጥን አውቶቡስ የአካል ለውጥ በማድረግ “ሳፋሪ ባስ” የተሰኘች ለቱሪስቶች አመቺ የሆነች ተሽከርካሪ ሰርቶ ለአገልግሎት ብቁ ያደረገ ሲሆን ልምዱን ለሌሎች መሰል ተቋማት ለማካፈል ዝግጁ እንደሆነ መምሪያው ገልጿል፡፡
መምሪያው ለውስጥ እና ለውጭ ደንበኞች የከባድ ተሽከርካሪዎች ጥገና አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን አሁን ላይ የውጭ ደንበኞቹ ቁጥር 22 ደርሷል፡፡ ጥቂቶቹን ለመግለጽ ያህል መስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፣ የመንግስት የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይገኙበታል፡፡

Light vehicle maintenance workshop
ቀን: Jan 1, 2025
ይህ ዎርክ ሾፕ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ የተደራጀ ሲሆን በቀን 35 መኪናዎችን የመጠገን አቅም አለው፡፡ የዚህ ወርክሾፕ መቋቋም ዋና ዓላማ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ዘርፈ

ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት ተስማሙ
ቀን: Dec 26, 2024
ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በግንባታ ግብዓት አቅርቦት እና በሌሎች መስኮች
ቀን: Dec 24, 2024
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) እና ራይዚንግ ሆንግፋ ኩባንያ መካከል በሽርክና የተቋቋመው ጎማን መልሶ መጠቀም የሚያስችል ፋብሪካ ከታህሳስ 09 ቀን 2017 ጀምሮ የሙከራ ምርት ማምረት ጀመረ፡፡ የፋብሪካና ምርት ጉዳዮች ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ቅዱስ ወ/ማርያም ለኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ባልደረቦች እንደተናገሩት ፋብሪካው ጥቅም ከሰጡ ጎማዎች ሽቦዎችን አውጥቶ፣ ጎማውን ቆራርጦ እና ፈጭቶ በቀን እስከ 600 ኪሎ ግራም የጎማ ዱቄት ማምረት ይችላል፡፡ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ይህ ፋብሪካ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ የጎማ ጡቦችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመሮጫ መሞችን እና የህጻናት መጫወቻ ቦታዎችን መስራት እንደሚያስችል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የቃሊቲ ኢንዱስትሪ ዞን የተተከለው ፋብሪካ እስከ አሁን ድረስ ከ30 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደፈጠረ ከኢንጂነሩ ገለጻ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አገልግሎት የሰጠ ጎማን መልሶ መጠቀም የሚያችል ፋብሪካ ሥራ ጀመረ
Deputy PM Visits Corporation’s Industry Zone
ቀን: Dec 14, 2024
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ( ኢ.ኮ.ሥ.ኮ) ካነገበው ራእይ እና ተልእኮ አንጻር በአፍሪካ ምርጥ ሦስት የኮንስትራክሽን እና ማኑፋክቸሪንግ ኩባንያዎች መካከል
Flexi Flume Factory
ቀን: Dec 5, 2024
የፍሌክሲ ፍሉም ፋብሪካ በቀድሞው የኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ድርጅት በ1999 ዓ.ም የተቋቋመ ፋብሪካ ሲሆን የስኳር ፋብሪካዎችን የፍሌክሲ ፍሉም ፍላጎት ለማሟላት ታልሞ የተመሰረተ ኩባንያ ነበር፡፡ በሒደት በተፈጠሩ የተለያዩ ምክንያቶች ፋብሪካው ትኩረት ተነፍጎት ማምረት ያቆመባቸው ጊዚያት ነበሩ፡፡ ይሁን እንጂ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ሦስት የተለያዩ የመንግስት ተቋማት በማዋሃድ በ2008 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን መመስረትና በ2012 ዓ.ም ኮርፖሬሽኑ ባከናውነው የሪፎርም ሥራዎች ህይወት ከዘራባቸው ጉዳዮች አንዱ የፍሌክሲ ፍሉም ፋብሪካ እንደ አዲስ ወደ ሥራ መግባትና ወደ ምርት መሸጋገር ነው፡፡
ኮርፖሬሽኑ ከተመሰረተ በኋላ የገበያ ፍላጎቱን ግምት ውስጥ በማስገባት የፍሌክሲ ፍሉም ፋብሪካን እንደ አዲስ እንዲከፈት ከማድረጉም በተጨማሪ በአሁኑ ሰዓት የተለያየ መጠን ያላቸው የአፈርና የእህል መያዣ/ከረጢቶች፣ ለተለያዩ የኮንስትራክሽን ሳይቶች ከለላ የሚሆኑ ሸራዎችንና ለመስኖ አገልግሎት የሚሆኑ ፓይፖችን አምርቶ ከመጠቀም ባለፈ ከውጪ የሚገቡ የአፈርና የእህል ማዳበሪያ ከረጢቶችን በሀገር ውስጥ አምርቶ ለገበያ በማቅረብ የውጪ ምንዛሬን እያዳነ ይገኛል፡፡
በተለይ የአፈር ማዳበሪያን ከወደብ ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቶ ለማከፋፈል የሚያገለግሉ የአፈር ማዳበሪያ ከረጢቶችን አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ በትኩረት እየሰራ ሲሆን የሙከራ ምርቶችን የማምረት ሥራ አከናውኗል፡፡ ምርቶችን በሚፈለገው መጠን ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ በፈረቃ የማምረት ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የፍሌክሲ ፍሉም ፋብሪካው ስድስት ማሽኖች ያሉት ሲሆን በቀን በእያንዳንዱ ማሽን ሦስት ሺህ በድምሩ 18 ሺህ ከረጢት ማዳበሪያዎች እና 18 ሺህ ብትን ከረጢት(ሺት) ያመርታል፡፡ በተጨማሪም በሰዓት 255 ሸራ (ላምኔትድ ፒፒ) በኬጅ እና በሰዓት ሦስት ሺህ ፍሌክሲ ፍሉም ፓይፕ በማምረት ላይ ይገኛል፡፡